Discoverየዓለም ዜና
የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

Author: DW

Subscribed: 7Played: 362
Share

Description

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።
763 Episodes
Reverse
• 103 ህገ ወጥ ኤርትራዊያን ስደተኞች እና 5 የሰዎች አዘዋዋሪ ደላሎች በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ ፡፡ • እስራኤል ለሶማሊ ላንድ የሰጠችው ዕውቅና ለዓለም እና ለቀጣናው ደህንነት እና መረጋጋት ስጋት መደቀኑን የሶማሊያው ፕሬዚዳንት ሀሰን ሼክ መሐመድ ተናገሩ ። • ጣልያን ለፍልስጤማዉያኑ ታጣቂ ቡድን ሐማስ የገንዘብ ድጋፍ ሲያደርጉ ነበር ያለቻቸውን 9 ሰዎች በቁጥጥር ስር ማዋሏን አስታወቀች። • የዩክሬይኑ ፕረዚደንት ቮለደሚር ዘለንስኪ ደም አፋሳሹን ጦርነት ለማስቆም አጋሮቻቸው በሩስያ ላይ ጫናቸውን እንዲያበረቱ ጥሪ አቀረቡ።
በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል ታጣቂዎች በወርቅ እና በእምነበረድ ማውጫ ሥፍራዎች ላይ በፈጸሙት ጥቃት ስምንት ሰዎችን ገደሉö የአፍሪካ ሕብረት፤ እስራኤል ለሶማሊላንድ ነጻ ሉአላዊት ሐገር አድርጋ እውቅና መስጠቷን አወገዘ። ሩስያ በዩክሬይን ዋና ከተማ ክዬቭ በፈጸመችው የሚሳይልና የድሮን ጥቃት 1 ሰው ሲሞት ከ20 በላይ መቁሰላቸው ተሰማ።
ሶማሊያ ውስጥ በተካሄደው የአካባቢዊ ምርጫ ከ500 ሺህ በላይ መራጮች መሳተፋቸው ተገለጸ። እስራኤል ለራስ ገዟ ሶማሊላንድ ዛሬ በፋ የሀገርነት እውቅና ሰጠች። ሶማሊላንድ የእስራኤልን እርምጃ ታሪካዊ ብላዋለች። አሸባብ የተሰኘው ጽንፈኛ ቡድን ለሶማሊያም ሆነ ለአካባቢው ሰላምና መረጋጋት ከፍተኛ ስጋት ነው ሲሉ የተመድ ባለሙያዎች አሳሰቡ። በደቡባዊ የመን ለመገንጠል የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች ሳውድ አረቢያ በዛሬው ዕለት ሠራዊታቸውን በአየር ጥቃት ደበደበች ሲሉ ከሰሱ። ዩናይትድ ስቴትስ ትናንት ምሽት ሰሜን ምዕራብ ናይጀሪያ አካባቢ በሚንቀሳቀሰው እራሱን እስላማዊ መንግሥት በሚለው ታጣቂ ቡድን ይዞታ ላይ የአየር ድብደባ አካሄደች።
• በጋምቤላ ክልል እየተባባሰ በሄደው ግጭት ስጋት እንደገባው ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን በእንግሊዘኛ ምህጻሩ MSF አስታወቀ ። • ታንዛንያው ውስጥ በሚገኘው የኪሊማንጃሮ ተራራ ላይ ሄሌኮፕተር ተከስክሶ የአምስት ሰዎች ህይወት አለፈ። • ሶማሊያዉያን ለአካባቢ ምርጫ መዲናዋ ሞቃዲሾ ውስጥ ድምጽ ሲሰጡ ዋሉ ። • በኢንተር ፖሊስ ለአመታት ሲታደን የነበረው ኤርትራዊው ኪዳነ ዘካሪያስ ሃብተማሪያም ኔዘርላንድስ መዲና አምስተርዳም ውስጥ ፍርድ ቤት ሊቀርብ ነው። • የሮማ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ሊዮ አስራ አራተኛ በተለይ የዩክሬን እና ጋዛ ጦርነቶችን «ትርጉም አልባ» ሲሉ አወገዙ ።
ጋምቤላ ከተማን ጨምሮ የፀጥታ ችግር በሚስተዋልባቸው የክልሉ አካባቢዎች የሰዓት እላፊ ገደብ ከዛሬ ምሽት ሁለት ሰዓት ጀምሮ መጣሉ ተገለጸ። ዩናይትድ ስቴትስ አራት አዲስ ዓለም አቀፍ የጤና የመግባቢያ ስምምነቶችን ከአራት የአፍሪቃ ሃገራት ጋር ተፈራረመች። በቱርክ አንካራ አቅራቢያ በተከሰከሰ አውሮፕላን ውስጥ የነበሩ የሊቢያ ጀነራሎች እና የልዑካን ቡድናቸው ሕይወት ማለፉ ተነገረ። ሦስቱ የበረራ ሠራተኞችም አልተረፉም። ዩናይትድ ስቴትስ የቀድሞ የአውሮፓ ሕብረት ኮሚሽነርን ጨምሮ በአምስት አውሮጳውያን ላይ የጣለችውን የቪዛ እገዳ የአውሮጳ ሕብረት፤ ጀርመን እና ፈረንሳይ አወገዙ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ቀጣዩን ሀገር አቀፍ ምርጫ አስመልክቶ በምርጫ አስቻይ ኹኔታ እና መሠል ጉዳዮች ላይ ትናንት ገዢው ብልጽግና ፓርቲን ጨምሮ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ተወካዮች ጋር ተወያይቷል።የየመን ሁቲ አማጽያንና በአለም አቀፉ ማሕበረሰብ ቅቡልነት ያለውና አሁን የመንን እየመራ ባለው መንግስት መካከል በተደረገው ድርድር ከሁለቱም በኩል ወደ 3,000 የሚሆኑ የጦር እስረኞችን ለመልቀቅ ተስማሙ።ንብረትነቱ የሜክሲኮ የባሕር ሐይል የሆነና ለሕክምና አገልግሎት የሚንቀሳቀስ አንስተኛ አውሮፕላን ዛሬ ተከስክሶ ቢያንስ 5 ሰዎች መሞታቸው ተሰማ።
የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢህአፓ) በትግራይ ክልል መጠለያ ውስጥ የሚገኙ ወገኖች ለረሀብ መጋለጣቸውን አመለከተ። በረሀብ ላይ ለሚገኙት ወገኖች መንግሥትን ጨምሮ ሁሉም አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ እንዳለበት፤ የተፈናቀሉትም ወደ የቀያቸው መመለስ እንዳለባቸውም አሳስቧል። የናይጀሪያ መንግሥት በቅርቡ ታግተው ከነበሩ የቀሩትን 130 ልጆች ማስለቀቁን አስታወቀ። በዛሬው ዕለት ቤተሰቦቻቸውን ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል። በዛሬው ዕለት በሩሲያ ዋና ከተማ ሞስኮ በተከሰተ የቦምብ ፍንዳታ አንድ የሀገሪቱ ጀነራል ተገደሉ። ኢራን የሚሳኤል መርኀግብሯ መከላከያ እና የሚቃጣባትን ጥቃት ለማስቆም የተነደፈ መሆኑን አሳሰበች።
ወደ ጋምቤላ በቂ የጸጥታ አካላት በአስቸኳይ እንዲሰማሩ ኢሰመኮ አሳሰበ ፤ ደቡብ አፍሪቃ ፤ ቢያንስ ዘጠኝ ሰዎች በታጣቂዎች ጥቃት ተገደሉ ፤ የእስራኤል ካቢኔ እስራኤል በኃይል በያዘችው የፍልስጤም ግዛት የዮርዳኖስ ወንዝ ምዕራባዊ ዳርቻ 19 አዳዲስ የሰፈራ መንደሮች እንዲቋቋሙ አፀደቀ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ከቬንዙዌላ የባህር ዳርቻ ለሁለተኛ ጊዜ ድፍድፍ ዘይት የጫነ መርከብ በቁጥጥሯ ስር አዋለች፤
የሱዳን ጠቅላይ ሚኒስትር ካሚል ዒድሪስ ጦርነት በሚካሔድባቸው አካባቢዎች ሰብአዊ ርዳታ በሚቀርብበት ሁኔታ ላይ ከተባበሩት መንግሥታት ዋና ጸሀፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ እና ሌሎች ባለሥልጣናት ጋር ለመነጋገር ወደ ኒው ዮርክ አቀኑ። የናይጄሪያ ፕሬዝደንት ቦላ ቲኑቡ የሀገራቸውን የጸጥታ ተቋማት በከፍተኛ ሁኔታ ለማጠናከር ቃል ገቡ። አንድ ኤርትራዊን ጨምሮ አራት ሰዎች ባለፈው አንድ ሣምንት በዩናይትድ ስቴትስ የፍልሰት እና የጉምሩክ መስሪያ ቤት በእስር ላይ ሳሉ መሞታቸውን የሀገሪቱ መንግሥት መረጃ ይፋ አደረገ። የአፍሪካ ዋንጫ የእግር ኳስ ጨዋታ ከጎርጎሮሳዊው 2028 በኋላ በየአራት ዓመቱ እንደሚካሔድ ተወሰነ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ ማሕሙድ በአዲስ አበባ ተገናኙ። በኢትዮጵያ ለስደተኞች የሚደረገው ድጋፍ ከውድቀት አፋፍ እንደሚገኝ መንግሥት እና አራት ድርጅቶች አስጠነቀቁ። በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ ሊባባስ እንደሚችል የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ባልደረባ ሥጋታቸውን ገለጹ። ስዊድን በኤርትራ ላለፉት 24 ዓመታት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሐቅ በሕይወት እንዳለ ገለጸች። የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሌሎች ሀገር ዜጎች ቋሚ የአሜሪካ የመኖሪያ ፈቃድ በዕጣ የሚያገኙበትን የዲቪ ሎተሪ ፕሮግራም ሊያቆም ነው።
ጋምቤላ፥ ከፖሊስ አዛዥ ግድያ በኋላ በከተማዪቱ ሥጋቱ እንዳየለ ነው፤ አጣዬ፥ የአማራና ኦሮሞ ማኅበረሰብ ሰላም በማውረድ በጋር ማረስና መሥራት ጀመሩ፤ ዋጋዱጉ፥ቡርኪና ፋሶ በቁጥጥር ስር አውላቸው የነበሩ 11 የናይጄሪያ አየር ኃይል አባላትን ለቀቀች፤ ዋሽንግተን፥ የአሜሪካ ባለሥልጣናት በደቡብ አፍሪቃ መታሰራቸውን የአገሪቱ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አወገዘ፤ ብራስልስ፥ በአውሮጳ ኅብረት ጉባኤ የታገደው የሩስያ ሐብት ዋነኛው አጀንዳ ነው፤ ኪዬቭ፥ በጎርጎሪዮሱ 2026 እስከ 50 ቢሊዮን ዩሮ የበጀት ክፍተት እንዳለባት ዐሳወቀች
• የፕሪቶሪያ ስምምነት በሙሉ ተፈጻሚ አለመሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ለቀጠለው ግጭት አንዱ ምክንያት መሆኑን የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ጉባኤ አስታወቀ። • የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ወይም በእንግሊዘኛ ምህጻሩ አር ኤስ ኤፍ በዳርፉሯ የኤል ፋሽር ከተማ የጅምላ ጭፍጨፋ እና የአካል ማጉደል ተግባር መፈጸሙን የሚያረጋግጥ አዲስ ዘገባ ይፋ ሆነ። • የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ፍልስጥኤማዉያንን ጨምሮ ከሰባት በላይ ሃገራት ላይ የጉዞ ዕቀባ ጣሉ። • በአውስትራሊያ የቦንዲው የባሕር ዳርቻ ጥቃት የተጠረጠረው ግለሰብ 15 የግድያ ክሶችን ጨምሮ በ59 ወንጀሎች ክስ ተመሰረተበት ።
አርስተ ዜና፤ --ኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮችና ፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ረቡዕ በሚያካሂደዉ የጋራ ስብሰባ የሕንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ ንግግር እንደሚያደርጉ ታወቀ። ሞዲ መዲና አዲስ አበባ ገብተዋል።--ሱዳን በድጋሚ በዓለም አቀፍ የሰብዓዊ ቀዉስ መዘርዝር ቀዳሚ የዓለም ሃገር መሆንዋ ተገለፀ። ከሱዳን ቀጥሎ የፍልስጤም ግዛቶች ፤ኢትጵያና ሄይቲ በዓለም አቀፉ የሰብዓዊ ቀዉስ መዘርዝር 3ኛ ደረጃ ላይ በየተራ ተቀምጠዋል።--በሩሲያ እና በዩክሬን መካከል ያለውን ጦርነት ለማስቆም እየተካሄደ ያለዉ ዉይይት እና ድርድር ፤ ለሰላም «ከምንጊዜውም በላይ ቅርብ ሆንዋል» ሲሉ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ተናገሩ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የዳሰነች ወረዳ መስተዳድር ለሁለተኛ ጊዜ የሕዝብ እንቅስቃሴ ገደብ መጣሉን አስታወቀ ፡፡ኤርትራ ያለፍርድ ያሰረቻቸውን ወደ 10,000 የሚገመቱ እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንድትፈታ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን አሳሰበ። ሳውዲ አረቢያ በመገባደድ ላይ ባለው ጎርጎሮሳዊ 2025 ዓመተ ምህረት የሞት ቅጣት በመፈጸም የዓለም ክብረወሰን መያዝዋን ዘገባዎች አመላከቱ።
በሱዳን በምትገን የዲሊንጅ ከተማ በሚገኝ አንድ ሆስፒታል በተፈጸመ የድሮን ጥቃት 7 ስቪሎች መገደላቸውን የሆስፒታል ምንጮች አስታወቁ። የእስራኤል ጦር በደቡብ ሊባኖስ «በኢራን ይደገፋል» ያለው የሒዝቦላህ አባላት ናቸው ያላቸውን 3 ታጣቂዎች መግደሉን አስታወቀ። በአውስትራልያ ቦንዲ በተበለ የባሕር ዳርቻ 2 ጠመንጃ የታጠቁ ግለሰቦች ዘመናት ያስቆጠረውን ባሕላዊ ክብረበ ዓላቸውን ሲያከብሩ በነበሩ ይሁዲዎች ላይ ዛሬ በፈጸሙት የተኩስ እሩምታ ቢያንስ 12 ሰዎች መሞታቸውን ተሰማ።
የኢትዮጵያ እና የኤርትራ “ሉዓላዊነት፣ ነጻነት እና የግዛት አንድነት እንዲከበር” ብሪታኒያ እና ቱርክን ጨምሮ አምስት ሀገራት በጋራ ጥሪ አቀረቡ። ሁለቱ ሀገራት “ማንኛውንም ውጥረት ወይም አለመግባባት በሰላማዊ እና በዲፕሎማሲያዊ መንገድ እንዲፈቱ” የአውሮፓ ኅብረት ጠይቋል። ኤርትራ ከምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ድርጅት አባልነት ራሷን ለማግለል ያሳለፈችው ውሳኔ እንዳሳዘናት ጅቡቲ አስታወቀች። ርዋንዳ በምሥራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የወሰደችው እርምጃ በዶናልድ ትራምፕ አሸማጋይነት በዋሽንግተን የተፈረመውን የሰላም ሥምምነት እንደሚጥስ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ አስታወቁ።
-ዶይቸ ቬለ (DW) ሁለት ዘጋቢዎቹ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን በቋሚነት መታገዳቸውን አጥብቆ ተቃወመ። ሰባቱ ጋዜጠኞች ስራቸዉን ቀጥለዋል። -ኢትዮጵያና ኤርትራ አንዳቸው የሌላውን የግዛት አንድነት እንዲያከብሩ የተመድ አሳሰበ። በሁለቱ ሀገራት መካከል“እንደገና የተቀሰቀሰዉ አዲስ ውጥረት” እንዳሳሰበውም ገልጿል። በሌላ በኩል ኤርትራ እራስዋን ከኢጋድ አባልነት አገደች።-የትራምፕ አስተዳደር በዩናይትድ ስቴትስ ለሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን ህጋዊ መኖርያ ፈቃድን በግዚያዊነት ማገዱን አስታወቀ።-ጀርመን በሰሜን ኢትዮጵያን ለሰላም ግንባታ፣ ለማረጋጋት እና ለግጭት መከላከል ጥረቶች የሚውል ተጨማሪ የ5 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ አደረገች።
ጋዜጠኛ እዮብ ሽመልስ በአስቸኳይ እንዲፈታ CPJ ጠየቀ፤ ከ400 በላይ ንፁሀን ዜጎች በምስራቃዊ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ተገደሉ፤ ዩናይትድ ስቴትስ የደቡብ ሱዳንን መንግሥትን አስጠነቀቀች፤ በክሮኤሺያ-ቦስኒያ ድንበር አቅራቢያ ጀልባ ሰምጣ ሶስት ስደተኞች ሞቱ፤ ዩናይትድ ስቴትስ ነዳጅ የጫነች የቬንዙዌላ መርከብ በቁጥጥሯ ስር አዋለች፤በዩክሩን ሰው አልባ አይሮፕላኖች የሩሲያ አይሮፕላን ማረፊያዎች ስራ ተስተጓጎለ
በከባድ የሙስና ወንጀል ጥፋተኛ ሆነው የተገኙት የኢትዮጵያ አደጋ ስጋት ሥራ አመራር የቀድሞ ኮሚሽነር አቶ ምትኩ ካሣ የ13 ዓመት እስራት ተፈረደባቸው። በዓለም የሰብዓዊ መብቶችን ለማስከበር የሚውለው የገንዘብ ድጋፍ እየቀነሰ፤ ፀረ መብት ለሆኑ እንቅስቃሴዎች የሚደረገው የገንዘብ ድጋፍ እየጨመረ መሆኑን የተመድ አመለከተ። ሩዋንዳ ዴሞክራቲክ ኮንጎ እና ቡሩንዲ ሆን ብለው የሰላም ስምምነቱን እየጣሱ ነው ስትል ከሰሰች። ዴሞክራቲክ ኮንጎ በበኩላ ዩናይትድ ስቴትስ ሩዋንዳን አደብ ታስገዛልኝ ብላለች። ሩሲያ የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ከምዕራብ ሃገራት መሪዎች ብቸኛው የሰብአዊ መብቶች ጉዳይ የሚገዳቸው መሪ ናቸው አለች።
ኢትዮጵያ የተመድ የሰብዓዊ መብቶች ም/ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ሆና መመረጧ፤ ከአማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት አፋሀድ ሰብሳቢ እስክንድር ነጋ የተደረገ ቃለ መጠይቅ ፤ ብሔራዊ የምርጫ ቦርድ የመጪውን ምርጫ ቀን ይፋ ማድረጉ
loading
Comments 
loading