Discoverየዓለም ዜና
የዓለም ዜና

የዓለም ዜና

Author: DW

Subscribed: 7Played: 362
Share

Description

ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።
815 Episodes
Reverse
የየካቲት 10 ቀን 2019 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊትና የትግራይ ክልል ኃይሎች በትግራይ ክልል ድንበር ላይ በብዛት እየሰፈሩ ነው ሲሉ አንድ ዲፕሎማት መናገራቸውን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት AFP ዘገበ። ማንነታቸውን ያልተገለጸው ዲፕሎማቱ «የፌደራሉ ሠራዊት ትግራይን ከቧል ፤« የትግራይ ክልል ኃይሎችም ድንበሮቻቸው ላይ እየሰፈሩ ነው» በማለት ተናግረዋል። የቱርክዬ ፕሬዝዳንት ረጀብ ተይፕ ኤርዶሃን ዛሬ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት አዲስ አበባ ገብተዋል። በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ በተቀሰቀሰ ግጭት 15 ሰዎች መገደላቸውን ነዋሪዎችና አንድ የምክር ቤት አባል ተናገሩ።
• በዋነኛው የኬንያው ጆሞኬንያታ አውሮፕላን ማረፊያ በተቀሰቀሰ የሥራ ማቆም አድማ በረራዎች ተስተጓጎሉ ። • የናይጄሪያ ጦር በቦርኖ ግዛት የተሰነዘረበትን የተቀናጀ የሽብር ጥቃት መመከቱን አስታወቀ። • የእስራኤል መንግሥት በምዕራባዊ የዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ የሚገኝ ሰፊ መሬት «የመንግሥት ንብረት» አድርጎ ለመመዝገብ የወሰነው ውሳኔ ከፍተኛ ተቃውሞ ቀሰቀሰ። • ጀርመን በየብስ ድንበሮቿ ላይ የምታደርገውን ጥብቅ የስደተኞች እና የጸጥታ ቁጥጥር ለተጨማሪ ስድስት ወራት አራዘመች። • ሩሲያና በዩክሬንን ወደ ድ ለማምጣት ብቸኛዋ አቅም ያላት ሀገር አሜሪካ መሆኗን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ ተናገሩ።
39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ዛሬ ተጠናቀቀ።ባለፈው ጥቅምት ወር ሱዳን ውስጥ ከ6,000 በላይ ሰዎች በሦስት ቀናት ውስጥ ተገደሉ። የሙኒክ የጸጥታ ጉባኤ ተጠናቀቀ። የዩናይትድ ስቴትስ ህንድ ውቅያኖስ ላይ የነዳጅ መርከብ በቁጥጥር ስር አዋለች።ዩክሬን በሰው አልባ አይሮፕላን አንድ የሩሲያ ነዳጅ ማከማቻን አቃጠለች።
በአፍሪካ “ግልጽ እና ድብቅ ግጭቶች ሥር እየሰደዱ” መምጣታቸውን “ሕገ-መንግሥታዊ ያልሆኑ የመንግሥት ለውጦች” ማንሠራራታቸውን የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ ተናገሩ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ ኢትዮጵያ የባሕር በር ልታገኝ ይገባል የሚል አቋማቸውን ለ39ኛው የአፍሪካ የመሪዎች ጉባኤ ገልጸዋል። ስድስት የግል ባንኮች ድርሻዎቻቸውን በካፒታል ገበያ ለማስመዝገብ መቃረባቸውን የኢትዮጵያ ሰነደ ሙዓለ ንዋዮች ገበያ ይፋ አደረገ። የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት ጆንጊሌ እና ምሥራቅ ኢኳቶሪያ ግዛቶችን ጨምሮ በመላ ደቡብ ሱዳን ግጭት መባባሱ እጅግ እንዳሳሰበው አስታወቀ።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለስልጣን የሮይተርስ የጋዜጠኖች ቡድን የአፍሪካ ሕብረት ስብሰባ እንዳይዘግቡ ፍቃድ መከልከሉን የዜና ወኪሉ አስታወቀ። በአማራ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ከጥር መጨረሻ ጀምሮ በከባድ የጦር መሣሪያ የታገዘ ግጭት መኖሩን ነዋሪዎች፣ ማኅበራት እና የዞኑ ፖሊስ ገለፁ። የኢራን መንግስት በሰላማዊ በሰልፈኞች ላይ የተወሰደውን የሐይል እርምጃ የሚመረምር ገለልተኛ አጣሪ ቡድን አቋቋመ። አሜሪካ ሁለተኛዋ ግዙፍ የጦር አውሮፕላን ተሸካሚ መርከብ ወደ መካከለኛ ምስራቅ እንደምትልክ ተሰማ።
• የአፍሪካ ህብረት በሱዳን እና በሶማሊያ የሚደረጉ የውጭ መንግስታት ጣልቃ ገብነትን አስጠነቀቀ። • ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ጣቢያዎች ዝርዝር በትግራይ ክልል ሥር አድርጎ ያወጣው፣ ቦርዱ ከዚህ በፊት ሲጠቀምበት የነበረውን "የምርጫ ክልል አደረጃጀት" በመከተሉ መሆኑን አስታወቀ። • በሰሜናዊ ሱዳን በአባይ (ናይል) ወንዝ ላይ በደረሰ የጀልባ መስጠም አደጋ በትንሹ 21 ሰዎች መሞታቸውን የአካባቢው ባለስልጣናት አስታወቁ። • የግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ ኤል-ሲሲ አሽራፍ ሳሌምን አዲሱ የመከላከያ ሚኒስትር አድርገው ሾሙ። • በማዳጋስካር በደረሰ አውዳሚ አውሎ ነፋስ የ31 ሰዎች ሕይወት አለፈ። በ
-ሰሜን ኢትዮጵያ ዉስጥ ዳግም ጦርነት ይጫራል ብለዉ በመሥጋት ከየቀያቸዉ የሸሹ የአለማጣ፣ የኮረምና የአካባቢዉ ነዋሪዎች የሰብአዊ ርዳታ እንዲደረግላቸዉ ጠየቁ።ከ60ሺሕ የሚበልጡት ነዋሪዎች ከየቀያቸዉ የሸሹት ከሁለት ሳምንት በፊት የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አካባቢዉን ልቅቆ በመዉጣቱ ነዉ። -የደቡብ ሱዳን ተቀናቃኝ ኃይላት የገጠሙት ጠብ በአዲሲቱ አፍሪቃዊት ሐገር የከፋ ደም መፋሰስ ሊያስከትል እንደሚችል የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስጠነቀቀ።-የኢራን እስላማዊ አብዮተኞች ሥልጣን የያዙበት 47ኛ ዓመት በጦርነት ሥጋት፣ በዛቻና ተቃዋሞ መሐል ዛሬ ተከብሮ ዋለ።
ቤኒሻንጉል፥ ኢትዮጵያ እና ሱዳን ድንበር ውስጥ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች ማሰልጠኛ መገንባቱ ተዘገበ፤ ጄኔቫ፥ ተመድ በትግራይ ክልል ውጥረቱ እንዲረግብ ጥሪ አስተላለፈ፤ አ.አ፥ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በግማሽ ዓመት 4.4 ቢሊዮን ዶላር ገቢ ማግኘቱን ይፋ አደረገ፤ ባሕር ዳር፥ በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱ 19 የፖለቲካ ፓርቲዎች ለ7ኛው አገራዊ ምርጫ ዝግጁ መሆናቸውን ገለጹ፤ ጄኔቫ፥ ተመድ ሱዳን ውስጥ ሕጻናት ለከፍተኛ ረሐብ ተጋልጠዋል ሲል አስጠነቀቀ፤ በሊቢያ የባሕር ጠረፍ በደረሰ የጀልባ አደጋ 53 ስደተኞች መሞታቸው አለያም መጥፋታቸው ተዘገበ
ኤርትራ ከኢትዮጵያ ግዛት ሰራዊቷን እንድታስወጣና ከኢትዮጵያ አማጽያን ጋር የምታደርገውን ማንኛውም ትብብር እንድታቆም በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የቀረበላትን ጥሪ ውድቅ አደረገች። ሶማሊያና ሳውዲ ዓረቢያ የጋራ ወታደራዊ ትብብር ለማድረግ መስማማታቸውን የሶማሊያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። ሱዳን ወደ የምስራቅ አፍሪካ የልማት በይነመንግስታት (ኢጋድ) እንደምትመለስ አስታወቀች። አለፈው ሳምንት በሞስኮ በአንድ የሩስያ ጀነራል በተፈጸመው የግድያ ሙከራ የፖላንድ እጅ አለበት ሲል የሩስያ የአገር ውስጥ የስለላ መስሪያቤት አስታወቀ።
• ኤርትራ በአስቸኳይ ሰራዊቷን ከሉአላዊ ግዛቶቿ እንድታስወጣ ኢትዮጵያ አሳሰበች። • በሰሜናዊ ናይጄሪያ ካዱና ግዛት ታጣቂዎች በአንድ የኃይማኖት አባት መኖሪያ ላይ በፈጸሙት ጥቃት ሦስት ሰዎች ተገደሉ። • ደቡብ አፍሪቃ በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የሚገኙ የተባበሩት መንግስታት የሰላም አስከባሪ ወታደሮቿን ልታስወጣ ነው። • አሜሪካ በትውልድ ሃገራቸው መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ በማሴር የጦር መሣሪያ ሲያዘዋውሩ ደርሼባቸዋለሁ ያለችውን ደቡብ ሱዳናዊ በእስራት ቀጣች። • በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረሱ ስምምነቶች ዋጋ አይኖራቸውም ሲሉ አንድ የእስራኤል ሚንስትር ተናገሩ ።
የዛሬው የዓለም ዜና፤ በኢትዮጵያ ሕፃናት ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች አሳሳቢ ደረጃ ላይ ደርሷል መባሉን፣የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል በፈጸመው የድሮን ጥቃት ህጻናትን ጨምሮ 24 ሰዎች መገደላቸውን ፣የየመን የአመራር ምክር ቤት ኃላፊ በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል አዲስ ካቢኔ መሰየሙን፤ጀርመን በቅርብ ጊዜ በተከሰቱ ቀውሶች ወደ 1 ትሪሊዮን ዩሮ ማውጣቷን ጥናት ማመልከቱን፤ትራምፕ ኦባማን በተመለከተ የለጠፉትን የዘረኝነት ቪዲዮ ከማኅበራዊ ገፃቸው ማጥፋታቸውን እንዲሁምሩሲያ ከ400 በላይ በሆኑ ድሮኖች እና በ40 ሚሳይሎች የዩክሬንን የኃይል ማመንጫዎች መምታቷን ያስቃኛል።
ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት እና በህወሓት መካከል የበረታውን ውጥረት ለመፍታት “የሰከኑ ውይይቶች” እንደሚያስፈልጉ አሳሰበች። የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ አባል የሆኑት ዶክተር ደሳለኝ ጫኔ በመጪው ግንቦት በሚካሔደው ሀገራዊ ምርጫ እንደማይሳተፉ አስታወቁ። በዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ በአውሮፕላን ማረፊያ ላይ የተፈጸመው የድሮን ጥቃት “የሽብር ድርጊት” ሊባል እንደሚችል የአፍሪካ ኅብረት አስታወቀ። በፓኪስታን ዋና ከተማ ኢዝላማባድ በአንድ መስጂድ ውስጥ አጥፍቶ ጠፊ በፈጸመው ጥቃት 31 ሰዎች ሲገደሉ ከ170 በላይ ቆሰሉ። የሩሲያ ጦር ሠራዊት የወታደራዊ ሥለላ ምክትል ኃላፊ በሞስኮ በጥይት ተመተው ቆሰሉ።
አአ፥ የምርጫ ቦርድ ምርጫ የሚካሄድባቸው የፀጥታ ኹኔታ አረንጓዴ፣ ቢጫ እና ቀይ፤ ዋሽንግተን፥ ተመድ የኖቤል የሰላም ተሸላሚን የሰው ሠራሽ አስተውሎት 40 ተከታታዮች ቡድን አባል አደረገ፤ ዋሽንግተን፥ ተመድ የኖቤል የሰላም ተሸላሚን የሰው ሠራሽ አስተውሎት 40 ተከታታዮች ቡድን አባል አደረገ፤ ላጎስ፥የናይጄሪያ መንግሥት እስላማዊ ታጣቂዎች ላይ አዲስ ዘመቻ መክፈቱን ዐሳወቀ፤ ላጎስ፥የናይጄሪያ መንግሥት እስላማዊ ታጣቂዎች ላይ አዲስ ዘመቻ መክፈቱን ዐሳወቀ፤ ዶሃ፥ የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሬድሪሽ ሜርትስ ከባሕረ ሠላጤው አገራት ጋር በመከላከያው ዘርፍ ትብብር፤ ካይሮ፥ ዳርፉር ረሐብ ተንሰራፍቷል ተባለ
• የኢትዮጵያ መንግስት በ2018 ከታቀደው ምርጫ በፊት በገለልተኛ መገናኛ ብዙሃን እና በሲቪል ማህበረሰብ ላይ የሚወስደውን እርምጃ አጠናክሮ መቀጠሉን የሰብአዊ መብት ተሟጋቹ ሂውማን ራይትስ ዎች ባወጣው አመታዊ ዘገባ አመለከተ። • ሶማሊላንድ በቅርቡ የሀገርነት እውቅና ከሰጠቻት እስራኤል ጋር በቅርቡ የንግድ አጋርነት ስምምነት ሃሳብ አቀረበች። • የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ በእንግሊዘኛ ምህጻሩ RSF በደቡባዊ ምስራቅ ይዞታዉን ኢትዮጵያን ወደ ሚያዋስኑ አካባቢዎች ማስፋቱን አስታወቀ። • ዕውቁ ኤርትራዊ የታሪክ ተመራማሪ ፕሮፌሰር አስምሮም ለገሰ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ ።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በትግራይ ጦርነት ወቅት ከመንግሥታቸው ወግኖ የተዋጋው የኤርትራ ጦር በአክሱም ከተማ “ወጣቶች በጅምላ” እንደረሸነ ለመጀመሪያ ጊዜ አመኑ። የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በባሕር ዳር ከተማ የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሐኪም የነበሩት ዶክተር አንዱዓለም ዳኜ ገዳይ በዕድሜ ልክ እስራት እንዲቀጣ ወሰነ። የሱዳን ጦር በመሐመድ ሐምዳን ደጋሎ የሚመራው ፈጥኖ ደራሽ ኃይል እና አጋሮቹ በካዱግሊ ከተማ ላይ ያደረጉትን ከበባ ሰበረ። ሩሲያ ለሊቱን በዩክሬን ላይ ከፍተኛ ጥቃት እንደፈጸመች ፕሬዝደንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ አስታወቁ።
• ከሰሞኑ በትግራይ ኃይሎች እና በፌዴራል መንግስቱ የጸጥታ ኃይሎች መካከል ተፈጥሮ በነበረው ግጭት ከተለያዩ ከተሞች የተፈናቀለው ህዝብ ቁጥር ከ60 ሺ በላይ መድረሱ ተገለጸ። • የብሪታንያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቬት ኩፐር ከአፍሪካ ቀንድ አካባቢ ወደ ሀገሪቱ ለመድረስ የሚሞክሩ ስደተኞች ቁጥር ለመቆጣጠር የሚያስችሉ እርምጃዎች ላይ ትኩረት ማድረጋቸውን አስታወቁ ። • በኒጀር መዲና የአየር ኃይል የጦር ሰፈር ባለፈው ዓርብ ለደረሰው ጥቃት ራሱን እስላማዊ መንግሥት ብሎ የሚጠራው በእንግሊዘኛ ምህጻሩ አይ ኤስ ኃላፊነት ወሰደ። • የናይጄሪያ ጦር ኃይል የጽንፈኛው ቦኮ ሃራም ታጣቂ ቡድን አዛዥ መግደሉን አስታወቀ።
በዛሬው የዓለም ዜና ፤ሕዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ ፤ህወሓት በፌደራል መንግሥት እና በትግራይ ሀይሎች መካከል ያለውን ችግር በንግግር ለመፍታት ዝግጁ መሆኑን መግለፁ።ብሪታኒያ ፤በትግራይ ኃይሎች እና በመከላከያ ሠራዊት መካከል የተቀሰቀሰውን ግጭት ተከትሎ ዜጎቿ ወደ ሁሉም የትግራይ ክልል አካባቢዎች እንዳይጓዙ ማስጠንቀቂያ መስጠቷን፣ እስራኤል በእስራኤ እና በሀማስ መካከል የተኩስ አቁም ስምምነት ሁለተኛ ምዕራፍ መጀመሩን ተከትሎ የራፋህ መሸጋገሪያ መንገድን በከፊል መክፈቷን፤ኢራን ከአሜሪካ ጋር ለመደራደር ጥረት እየተደረገ መሆኑን አንድ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣን ፍንጭ መስጠታቸውን፤ የተመለከቱ ርዕሰ ጉዳዮች ተካተዋል።
• የሶማሊያ እና የጂቡቲ መሪዎች ከጠቅላይ ሚንስትር አቢይ አህመድ ጋር ጂግጂጋ ውስጥ ተገናኙ ። • ትግራይ ክልል ውስጥ ተፈጸመ በተባለ የድሮን ጥቃት አንድ ሰው መገደሉ ተዘገበ። • በሰሜናዊ ናይጄሪያ ጽንፈኛ ታጣቂ ቡድኖች በተለያዩ አካባቢዎች ባደረሷቸው ጥቃቶች ሲቪሎችን ጨምሮ በርካታ ሰዎች ተገደሉ ። • ደቡብ አፍሪቃ እና እስራኤል አንዳቸው የሌላውን ከፍተኛ ዲፕሎማት በማባረር ዲፕሎማሲያዊ ውጥረት ውስጥ መግባታቸው ተነገረ።
አ.አ፥ የሰሜን ኢትዮጵያ ውጥረት ያሳሰበው የአፍሪቃ ኅብረት የቅርብ ክትትል እያደረገ ነው፤ ቤርሊን፥ የሱዳንን ጦርነት ለማስቆም የአዉሮጳ ሐገራት እንዲያግዙ የሱዳን ፖለቲከኞች ጠየቁ፤ ቤርሊን፥ የሱዳንን ጦርነት ለማስቆም የአዉሮጳ ሐገራት እንዲያግዙ የሱዳን ፖለቲከኞች ጠየቁ፤ ናይሮቢ፥ ዩናይትድ ስቴትስ ኬንያ ውስጥ የጦር ሠፈር ልታስፋፋ ነው፤ ቴሕራን፥ የዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራንን ፍጥጫ ባየለበት በአሁኑ ወቅት እሥራኤል ድርድሩ ቢቀጥል ትሻለች ተባለ፤ ቪዬና፥ የተመድ የአውቶሚክ ተቆጣጣሪ ቦርድ ዛሬ አስቸኳይ ስብሰባ አደረገ
የጥር 21 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ትግራይ ክልል ከተሞች ያደርግ የነበረውን የዕለቱን በረራ ዛሬ ካቋረጠ በኋላ ስጋት እንዳደረባቸው የመቀሌ ከተማ ነዋሪዎች ተናገሩ ። ነዋሪዎች በተለይ ለዶቼ ቬለ እንዳሉት በትግራይ እና በአጎራባች የአማራ ክልል አካባቢዎች ግጭት መቀስቀሱ አሰሳስቧቸዋል። ዩናይትድ ስቴትስ ለሶማሊያ የምትልከው የምግብ እርዳታ ላይ የጣለችውን እገዳ እንደምታነሳ አስታወቀች። የአውሮጳ ኅብረት በ15 የኢራን ባለሥልጣናት ላይ ማዕቀብ መጣሉን ዛሬ አስታወቀ። ኅብረቱ ማዕቀብ ከጣለባቸው ውስጥ የአብዮታዊ ዘብ ፈጥኖ ደራሽ ሰራዊት ዋና አዛዦችና ባለሥልጣናት ይገኙበታል።
loading
Comments