Discover
የዓለም ዜና
የዓለም ዜና
Author: DW
Subscribed: 7Played: 362Subscribe
Share
© 2025 DW
Description
ዶይቼ ቬለ የዕለቱን ዋና ዋና ዜናዎች ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በየቀኑ ያቀርባል። የኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ፖለቲካዊ እና ኤኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ጨምሮ የመላው ዓለምን ውሎ የተመለከቱ ጠቃሚ መረጃዎች በሰባቱም የሣምንቱ ቀናት ከምሽቱ አንድ ሰዓት ከዶይቼ ቬለ ያድምጡ። የዶይቼ ቬለን ዜናዎች በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ ማድመጥ ትችላላችሁ። የዶይቼ ቬለ ዜና በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በየዕለቱ በቀጥታ ይደመጣል።
730 Episodes
Reverse
-የሩስያ እና የዩክሬን ባለስልጣናት ከፍተኛ የሆነ ሰው አልባ አውሮፕላኖች ጥቃት መፈጸማቸውን በየበኩላቸዉ ገለፁ። ሩስያ መዲና ኪይቭ ላይ የድሮን ጥቃት አድርሳለች።
-የቦሮ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ከገዢው የብልጽግና ፓርቲ ጋር ለመዋሃድ የሚያስችለውን ውሳኔ አሳለፈ።
-አፋር ክልል የፈነዳዉ እሳተ ገሞራ የሚተፋዉ አመድ በሕንድ የሚደረግን የአዉሮፕላን በረራን አቋረጠ።
-የትራምፕ አስተዳደር ዩናይትድ ስቴትስ ወደ 235,000 የሚሆኑ ስደተኞችን የመኖርያ ፈቃድና ሁኔታቸዉን ሊፈትሽ መሆኑ ተሰማ።
የዛሬው የዓለም ዜና በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከሰላሳ በላይ ንጹሃን በታጣቂዎች መገደላቸውን፤ የሱዳን ጦር ኃይሎች አዛዥ የአሜሪካንን የእርቅ ሃሳብ ውድቅ አድርገዋል በሚል የተባበሩት አረብ ኢምሬቶች መውቀሷን፤የቀድሞ የደቡብ አፍሪቃ ፕሬዚዳንት ጃኮብ ዙማ ሴት ልጅ ያለፍላጎታቸው በዶንባስ እንዲዋጉ ሰዎችን ቀጥራለች በሚል መከሰሷን፤በጋዛ ሰርጥ አራት ፍልስጤማውያን መገደላቸውን የህክምና ባለሙያዎች መግለፃቸውን፤እስራኤል በጥቅምት 7ቱ የሀማስ ጥቃት ሀላፊነታቸውን አልተወጡም ያለቻቸውን ከፍተኛ የጦር አዛዦቿን ማባረሯን እንዲሁም ዝነኛው የሬጌ ሙዚቃ አቀንቃኝ ጂሚ ክሊፍ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።
ከናይጄሪያ የካቶሊክ ትምህርት ቤት ታግተው የተወሰዱ 50 ተማሪዎች ከአጋቾቻቸው ማምለጥ ቻሉ፤ የጀርመን መራሔ መንግሥት ሜርስ በቡድን 20 ጉባኤ ላይ ዩናይትድ ስቴትስ አለመሳተፏን ተቹ፤ ህንድ እና አጋሮቿ የኮፕ 30ን ውጤት አወደሱ፤የዩክሬን ጦርነት ለማቆም በቀረበው ምክረ ሐሳብ አሜሪካ እና የአውሮፓ መንግሥታት እየተወያዩ ነው
የዛሬው የዓለም ዜና ትግራይ ተጨማሪ ጥቃቶችን ለመከላከል መንግስታት እርምጃ መውሰድ አለባቸው ሲል ሂውማን ራይትስ ዎች ማሳሳቡን፤የደቡብ አፍሪካ ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ ዓለም አቀፍ ችግሮችን ለመፍታት በጋራ መተባበር እንደሚያስፈልግ ማሳሰባቸው፤ናይጄሪያ ውስጥ ከአንድ የካቶሊክ ትምህርት ቤት ከ300 በላይ ተማሪዎች በታጣቂዎች ታፍነው መወሰዳቸውን፤ዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በአሜሪካ የቀረበውን የሰላም እቅድ ላይ ከአውሮፓ አጋሮቻቸው ጋር መወያየታቸውን እንዲሁም አሜሪካ በኩባ ላይ የጣለችው ለአስርት አመታት የዘለቀ ማዕቀብ እንዲነሳ መጠየቁን ያስቃኛል።
በአማራ ክልል የባሕር ዳርና አካባቢው ከፍተኛ ፍ/ቤት፤ የጥበበ ጊዮን ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ሐኪም በነበሩት ዶ/ር አንዷለም ዳኘ ገዳይ ላይ የ25 ዓመት ጽኑ እስራት መወሰኑ፤ዩናይትድ ስቴትስ በG20 ስብሰባ ላይ እንደምትገኝ ደቡብ አፍሪቃ ማሳወቋ፤በናይጄሪያ ታጣቂዎች ከአንድ የከካቶሊክ ትምህርት ቤት ተማሪዎችን አፍነው መውሰዳቸውን፤ የአውሮፓ ህብረት መሪዎች ዶናልድ ትራምፕ የሩሲያ ዩክሬን ጦርነትን ለማስቆም ያቀዱትን የሰላም ሀሳብ እስካሁን በይፋ እንዳልደረሳቸው መግለፃቸው እንዲሁም ዶናልድ ትራምፕ እርሳቸውን የሚፃረር መልዕክት ባሰራጩ ዲሞክራቶች ላይ ሞት ቅጣት ለመቅጣት መዛታቸውን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።
-የኦሮሞ ነፃነት ግንባር (ኦነግ)ና የኦሮሞ ፌደራሊስ ኮንግረሰ (ኦፌኮ) በኦሮሚያ ክልል ያለዉን የፀጥታ፣ የሕግና ሥርዓት መደፍረስና መፋለሥ ለማቃለል ከክልሉ መሪዎች ጋር መነጋገር እንደሚሹ አስታወቁ።---የጀርመን መንግሥት ለአፍሪቃ ሕብረት አጀንዳ 2063 መርሐ-ግብር ማስፈፀሚያ ተጨማሪ 88 ሚሊዮን ዩሮ ለመርዳት ቃል ገባ።ተጨማሪዉ ገንዘብ አፍሪቃ ዉስጥ ዘላቂ ልማትን፣የአ,ረንጓዴ ኃይልን፣ሠላምና ፀጥታ ለማጠናከርና ለ,ጤና አገልግሎት እንደሚዉል በአዲስ አበባ የጀርመን ኤምባሲ አስታዉቋል።---ሕንድና ፓኪስታን ባለፈዉ ግንቦት የገጠሙት ዉጊያ የፈረንሳይና የቻይናን የጦር መሳሪያ ጥራትና አቅም ለመፈተሽ የዋለ እንደነበር ተነገረ
የህዳር 10 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
«ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት» በሚል መጠሪያ የተቀናጁት 5 ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች የኢትዮጵያ መንግስት ከምርጫው በፊት በሀገሪቱ ሰላም እና መረጋጋት እንዲያሰፍን ጠየቁ።
ከኤርትራ መሆንዋ ተነገረ የአንዲት እናት የተቆረጡ እጆችን አውራ ጎዳና ላይ ማግኘቱን የጀርመን ፖሊስ ዐሳወቀ። በቦንየተገን ጠያቂዎች ማቆያ የትኖር የነበረው ይህች እናት፣ የት እንዳለች እስከ ትናንት ድረስ እንደማያውቅ ፖሊስ ገልጿል።
በሱዳን ጦርነት ጣልቃ በመግባት የምትጠረጠረው የተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች በማኅበራዊ መገናኛ ዘዴዎች የሚደርስባት ወርጂብኝ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ሰ
አርስተ ዜናዎች፤
-ኢሕአፓ ባለፉት 7 ዓመታት በትግራይ ክልል ፣ በአፋር ክልልና በአማራ ክልል፣ አሁን ደግሞ በመላው የአማራ ክልልና በበርካታ የኦሮሚያ ክልል ቀጠናዎች ውስጥ፣ እየደረሱ ያሉ ያላቸውን የወገን ዕልቂትና የመሠረተ ልማት አውታሮች ብሎም የሌሎች ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረት ውድመት እንዲቆም ዛሬ ባወጣዉ መግለጫ ጠየቀ።-የሩሲያ ጦር በስድስት የአፍሪቃ ሀገራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን የሩሲያ ቴሌቪዥን ዘገበ።-የጀርመን መንግስት የእስራኤል በከፊል አቋርጦት የነበረዉን የጦር መሳርያ አቅርቦት ዉሳኔ እንደሚያነሳ አሳወቀ። በሌላ በኩል የጀርመን ለዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ጥበቃ ተጨማሪ 60 ሚሊዮን ዩሮ ሰጠች።
ደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ ሦስት ሰዎች በማርበርግ ተሐዋሲ መሞታቸውን የጤና ሚኒስቴር አረጋገጠ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በያዝነው ዓመት ለሚካሄደው 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ ፓርቲዎች ዕጩዎቻቸውን እንዲያስመዘግቡ ጥሪ አቀረበ።
የባንግላዴሽ ልዩ ችሎት በቀድሞዋ የሀገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር እና የሀገር ውስጥ ሚኒስትሩ ላይ የሞት ፍድር በየነ። የፖሊስ አዛዡ ደግሞ አምስት ዓመት እስራት ተፈርዶባቸዋል።
የሱዳን መንግሥት የተመ የሰብዓዊ መብቶች ምክር ቤት ዳርፉር አልፋሸር ውስጥ የተፈጸመውን ጥሰት የሚያጣራ ቡድን ለመላክ መወሰኑን ተቃወመ። በአንጻሩ ፈጥኖ ደራሹ ኃይል እውነቱን የሚያጣራው የልዑካን ቡድን እንዲላክ ጠይቋል።
የዛሬው የዓለም ዜና -ሊባኖስ የሚገኘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእስራኤል ጦር በሰላም አስከባሪዎች ላይ ተኩስ ከፈተ ማለቱን፤ ብሪታኒያ የስደተኞች ቁጥርን ለመቀነስ የጥገኝነት ፖሊሲ ማሻሻያ ማድረጓን፣ ምዕራብ ጀርመን ውስጥ የሚገኝ አንድ የጨረታ ቤት የሆሎኮስት ዕቃዎችን በሐራጅ ለመሸጥ ማቀዱ በጀርመን ቁጣ ማስነሳቱን፣ግሪክ እና ዩክሬን እስከ መጋቢት 2026 የሚዘልቅ የጋዝ ውል መፈራረማቸውን እንዲሁም በፊሊፒንስ በሙስና ምክንያት ታላቅ ተቃውሞ መቀስቀሱን ያስቃኛል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተከሰተው የሔሞራጅ ትኩሳት በሽታ መንስዔ የማርበርግ ቫይረስ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አረጋገጠ። በኢትዮጵያ የሚካሔደው ሀገራዊ ምክክር ያጋጠሙት “አብዛኞቹ ተግዳሮቶች ፖለቲካዊ በመሆናቸው ፖለቲካዊ መፍትሔ” እንደሚያስፈልጋቸው ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አሳሰቡ። ከሱዳን ሕዝብ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሰብአዊ ርዳታ ያስፈልገዋል ተባለ። ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን በይገባኛል በሚወዛገቡባት አቢዬ ግዛት የሰፈረውን ሰላም አስከባሪ የሥራ ዘመን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አራዘመ። ደቡብ አፍሪካ በኬንያ በኩል ወደ ጁሐንስበርግ የተጓዙ ፍልስጤማውያንን ጉዳይ እንደምትመረምር አስታወቀች።
-ታንዛኒያ ዉስጥ ባለፈዉ መስከረም የተደረገዉን አወዛጋቢ ምርጫ በሚቃወሙ የሐገሪቱ ዜጎች ላይ የተፈፀመዉ ግድያ እንደሚጣራ የሐገሪቱ ፕሬዝደንት አስታወቁ።ፕሬዝደንት ሳሚያ ሱሉሑ ሐሰን ዛሬ እንዳሉት የምርጫዉን ሒደት በመቃወማቸዉ ለታሰሩ ሰዎችም መንግሥታቸዉ ምሕርት ያደርጋል።-አፍሪቃ ዉስጥ በተገባደደዉ የግሪጎሪያኑ 2025 ዓመት የተሰራጨዉ የኮሌራ በሽታ 7ሺሕ ሰዎች ገደለ፤ ከ300 ሺሕ በላይ ለከፈ።-የሩሲያና የዩክሬን ጦር ኃይላት ዛሬ አንዱ የሌላዉን ግዛት በሰዉ አልባ አዉሮፕላንና በሚሳዬል ሲደበድቡ አነጉ።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጅንካ ከተማ የሄሞራጂክ ፊቨር በተባለ በሽታ 6 ሰዎች መሞታቸውን ተሰማ። የአፍሪካ ህብረት «በሰሜን ናይጄሪያ የተፈጸመ የዘር ማጥፋት ወንጀል የለም» ሲል አስተባበለ። እስራኤል በሐይል በያዘችው ምዕራባዊ የዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ የሰፈሩና «ፅንፈኛ» የተባሉ እስራኤላዉያን አንድ መስጊድን በእሳት ማቃጠላቸዉንና በመስጊዱ ግድግዳዎች ላይም «አጸያፊ» የተባሉ ፅሑፎች መጻፋቸው የፍልስጤማ ዜና አገልግሎት ዘገበ። ፈረንሳይ ከ10 ዓመታት በፊት በሽብር ጥቃት የተገደሉ 130 ዜጎችዋን ዛሬ ስትዘክር ዋለች።
ዛሬ ያስቻለዉ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የልደታ ምድብ ችሎት የቀድሞው የኢትዮጵያ የሰላም ሚንስትር ዴታ አቶ ታዬ ደንደአን ከ2 የክስ ጭብጦች ነጻ ሲያደርጋቸው በአንዱ ደግሞ ጥፋተኛ ብሏቸዋል።
ኢትዮጵያ ኮፕ 32ን ለማስተናገድ በዝግጅት ላይ መሆንዋን አስታወቀች። ጉባኤውን እንድታስተናግድ ያጸደቀውን የአፍሪቃ ተደራዳሪዎች ቡድንም አመሰገነች ።
ስደተኞችን የጫነች አንዲት የፕላስቲክ ጀልባ በሊቢያ የባህር ዳርቻ ሰጥማ ቢያንስ 42 ስደተኞች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ዓለም አቀፉ የፍልሰተኞች ጉዳይ ድርጅት በምህፃሩ IOM ዛሬ አስታወቀ። በግሪኳ ደሴት በጋቭዶስ አንዲት ስደተኞችን ያሳፈረች ጀልባ ሰጥማ ሦስት ሰዎች ሞቱ።
ኢትዮጵያ በጎርጎሪዮሳዊ 2027 ዓ.ም. ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ለውጥ ጉባኤን ለማስተናገድ ያቀረበችው ጥያቄ የበርካታ ሃገራትን ድጋፍ ማግኘቱ ተገለጸ። ይፋዊ ውሳኔው ዛሬ ብራዚል ላይ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል።
የተርክዬ አቃብያነ ሕግ የኢስታንቡል ከተማ ከንቲባ ከሁለት ሺህ ዓመት በላይ እንዲታሠሩ ጠየቁ።
በፓኪስታን ዋና ከተማ ኢዝላማባድ ላይ በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት 12 ሰዎች ተገደሉ። ሌሎች 27 ሰዎች ደግሞ ተጎዱ። ለድርጊቱ ኃላፊነት የወሰደ አካል የለም።
ሩሲያ ሌሎች የኒኩሊየር ኃይል ባለቤት ሃገራት የሚያደርጉ ከሆነ የኒኩሊየር ሙከራ እንደምታደርግ አስታወቀች።
ሕገወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ ነበር ተብለው የተጠረጠሩ ከ100 በላይ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር ዋሉ።
በበርካታ የታሪክ መፃህፍቶቻቸው የሚታወቁት አንጋፋው የታሪክ ምሁር ፕሮፌሰር ላጲሶ ጌታሁን ዴሌቦ በ87 አመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
ኢራን ሜክሲኮ ውስጥ የሚገኙትን የእስራኤል አምባሳደርን ለመግደል አሲራለች በማለት ዩናይትድ ስቴትስ ያወጣችውን ውንጀላ «እርባና ቢስ» ስትል አጣጣለችው።
የቢቢሲ ዋና ዳይሬክተርና የዜና ክፍል ሐላፊ በገዛ ፈቃዳቸው ስልጣናቸውን ለቀቁ። ሐላፊዎቹ ከሥልጣን የወረዱት የአሜሪካው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕን በተመለከተ በጣቢያው በተሰራ ዘጋቢ ፊልም ምክንያት ነው ተብሏዋል።
• ዩጋንዳ በቀጣዩ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላይ አሲረዋል ብላ ከአንድ ወር በፊት ያሰረቻቸውን ሁለት ኬንያዉያን አክቲቪስቶች ከእስር ለቀቀች።
• በስፔይኗ የቴኔሪፌ ደሴት የባህር ዳርቻ ትናንት ቅዳሜ በተነሳ ወጀብ የሶስት ሰዎች ህይወት አልፎ ሌሎች 15 ሰዎች መጎዳታቸውን የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት አስታወቀ።
• የአሜሪካ የሲቪል አቪዬሽን ባለስልጣን ለ14 ሰዎች ህልፈት ምክንያት ከሆነው የጭነት አውሮፕላን አደጋ በኋላ ተመሳሳይ ስሪት የሆኑ አውሮፕላኖች እንዳይበሩ አገደ።
• ዩክሬን በሩስያ የኃይል መሰረተ ልማት ላይ ባደረሰችው የአየር ጥቃት በበርካታ የአዋሳኝ አካባቢ ክልሎች ኃይል መቋረጡን ባለስልጣናት አስታወቁ።
DW Amharic -የዛሬው የዓለም ዜና ህወሓት በትግራይ ኃይል አባላት ላይ የድሮን ጥቃት መፈጸሙን መግለፁ።ህወሓት በገለፀው ትራምፕ በደቡብ አፍሪካ በሚካሄደው በG20 ጉባኤ ላይ የአሜሪካ ባለስልጣናት እንደማይገኙ መግለፃቸው፤የታንዛንያ ፖሊስ በሐገሪቱ ከተከሰተው ሁከትና ብጥብጥ ጋር በተያያዘ 10 የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች ለማሰር ማቀዱን ፣ሩስያ አንድ ተጨማሪ በምስራቅ የዩክሬይ ግዛት የምትገኝ መንደር መያዟን ማስታወቋን እንዲሁም ደቡብ ብራዚልን የመታው «ቶርኒዶ» የተሰኘው አውሎ ንፋስ 5 ሰዎችን ሲገድል ከ430 በላይ መጉዳቱ ያስቃኛል።
የጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዜጎች «የአካባቢያቸውን ልማት ማገዝ እንዲችሉ ሰላም ያስፈልጋል» ሲሉ ዛሬ ተናገሩ።
የሱዳን ጦር፣የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለሊቱን በሰሜን ምሥራቅ ሱዳን ሁለት ከተሞች ላይ የጣላቸውን የድሮኖች ጥቃቶች መመከቱን አስታወቀ። የጥቃት ዒላማ የአትባራ ከተማና ሪቨር ናይል ክፍለ ሀገር ናቸው።
ከበርካታ የአፍሪቃ ሀገራት የመጡ ከ1400 በላይ አፍሪቃውያን ከሩስያ ኅይሎች ጎን ተሰልፈው ይዋጋሉ ስትል ኪቭ አስታወቀች።
DW Amharic -የዛሬው የዓለም ዜና፤ በአፋር ክልል በትግራይ ሀይሎች መካከል የተቀሰቀሰው ግጭት ለጥቂት ቀናት ሲካሄድ የቆየ ነው መባሉን፤የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ ከ7ኛው አገር አቀፍ ምርጫ በፊት የሕገመንግሥት ማሻሻያ እንዲደረግ መጠየቃቸው፤አልፋሺር በሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሀይል ከተያዘች ወዲህ ሰባት ጋዜጠኞች የደረሱበት አለመታወቁን፤ሱዳን፤ የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉ በአሸባሪነት እንዲሰየም መጠየቋን፤ደቡብ አፍሪካ በሩሲያ ዩክሬን ጦርነት ውስጥ ተሳትፈው ከተያዙ ዜጎቿ የድረሱልኝ ጥሪ እንደደረሳት መግለጿን፤እስራኤል ከግብፅ ጋር በሚያዋስናት ድንበር ላይ የተዘጋ ወታደራዊ ቀጠና ማወጇን ያስቃኛል።























