DiscoverDW | Amharic - News
DW | Amharic - News
Claim Ownership

DW | Amharic - News

Author:

Subscribed: 53Played: 3,500
Share

Description

News, Analysis and Service from Germany and Europe - in 30 Languages
4747 Episodes
Reverse
ኃላፊነታቸውን ትላንት ሰኞ ከዶክተር እመቤት መለሰ የተረከቡት ዶክተር ኢሳያስ ካሳ በአስር ዓመታት ገደማ ውስጥ የኢትዮጵያ ልማት ባንክ አምስተኛ ፕሬዝደንት ሆነዋል። የባንኩ ፕሬዝደንት፣ የቦርድ ሰብሳቢ እና አባላት የተቀየሩበት የአመራር ለውጥ “ተቋማዊ ውጤታማነትን ለማሻሻል” ያለመ እንደሆነ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲንግስ ለዶይቼ ቬለ ገልጿል።
ባለፉት 3 ዓመታት በክልሉ ተፈጥሮ በቆየው የፀጥታ ችግርምክንያት የመምህራን ዝውውር ለማካሄድ አስቸጋሪ መሆኑንየሚገልፁት የደቡብ ወሎ ዞን ትምህርት መመሪያ ኃላፊ አቶአለምነው መኮነን በሰላም ቀጠናም ሆነ የፀጥታ ችግር ባለባቸው አካባቢዎች ያሉ መምህራን ዝውውሩን አጥብቀው ሲሹት ነበር ይላሉ
ኢዜማ በመጪው 7ኛው ሀገር አቀፍ ምርጫ እንደሚሳተፍ አቋሙን ለሕዝብ ይፋ ባደረገበትና የዛሬ መግለጫው ትምህርት ሚኒስቴር በሚፈጽማቸው ተግባራት "ያልተገበርነው ይኖራል እንጂ ከተተገበረው ውስጥ የኢዜማ ፖሊሲ ውስጥ የሌለ የለም" ብሏል።
በአሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ150 በላይ የታሸገ ውኃ የሚያመርቱ ፋብሪካዎች በሥራ ላይ እንደሚገኙ ከኢትዮጵያ የመጠጦች አምራች ኢንዱስትሪ ማሕበር የተገኘው መረጃ ያመለክታል። በተለይም የታሸጉ ውኃ የሚያመርቱ ፋብሪካዎች መበራከትን ተከትሎ የፕላስቲክ ብክለት አደጋ ተጋላጭነት እየጨመረ መጥቷል።
የበራስልሱ ስብሰባ ዩክሬን ጠንካራ ተደራዳሪ ልትሆን በምትችልበት የወታደራዊና የፋይናንስ እርዳታ ላይ ያተኮረ ሲሆን፤ በበርሊኑ ስብሰባ ለመጀመሪያ ግዜ አሚሪካ ፣ ዩክሬንና አውሮፓ በጋራ የሰላም ዕቅድ ላይ እንደተስማሙ ተገልጿል።
በኦሮሞ ፌዴራላዊ ኮንግረንስ (ኦፌኮ) በከፍተኛ አመራርነት ለዓመታት ያገለገሉ ፖለቲከኛ ደስታ ድንቃ ከፓርቲው መውጣታቸውን አረጋገጡ፡፡ ፖለቲከኛው ከሌሎች የትግል አጋሮቻቸው ጋር በመሆን በሌላ የፖለቲካ ድርጅት ለመምጣት መንገድ ስለመጀመራቸውም ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል፡፡
ሒውማን ራይትስ ዎች፦ የዶይቸ ቬለ ሁለት ወኪሎች በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለ ሥልጣን ለዘለቄታው መታገዳቸውን አወገዘ ። ለ«ኢትዮጵያ መንግሥት» ጥሪ ያስተላለፈው ሒውማን ራይትስ ዎች፦ «በዶይቸ ቬለ ጋዜጠኞች ላይ የጣለውን እገዳ በአስቸኳይ እንዲያነሳ፤ በመገናኛ ብዙኃን ላይ የሚያደርሰውን ተጨማሪ ጥቃት እንዲያቆም» ሲልም ጥሪ አስተላልፏል ።
የአፍሪቃ ቀንድ ቁልፍ አልያም ስልታዊ አቀማመጥ ላይ የሚገኝ ነው። ያም ሆኖ ግን ሥር በሰደደ አለመረጋጋት ይታወቃል።ከፍተኛ የወጣቶች ቁጥር ያለው ሆኖ ሳለም የሥራ አጥነትት ምጣኔው ሽቅብ የወጣበት መሆኑ የሚካድ አልሆነም። ቀጣናው መለያው ከዚህም ይሻገራል።
የማህበራዊ መገናኛ መድረኩ በእርግጥ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች የፈጠራ አቅማቸውንና ተሰጥኦዋቸውን እንዲያሳዩ፣ ከእኩዮቻቸው ጋር ትስስር እንዲፈጥሩና አዳዲስ የገቢ ማግኛ ሥልቶችን እንዲቀይሱ የዕድል በር መክፈቱ አይታበልም፡፡ ጥቂት የማይባሉ እዚህ ግባ ከማይባል ቦታ ተነስተው በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝና አትርፎላቸዋል።
ዶይቸ ቬለ (DW) ሁለት ዘጋቢዎቹ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን በቋሚነት መታገዳቸውን አጥብቆ ይቃወማል። የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን (EMA) ለዶይቸ ቬለ በጻፈው ደብዳቤ ከጋዜጠኞቹ ዘገባ ጋር በተያያዘ ተጨባጭ ምክንያት አልሰጠም።
ጾታን መሰረት ያደረገ ጥቃት በኢትዮጵያ ስር የሰደደ ችግር ቢሆንም፣ በአገሪቱ እየተከሰቱ ባሉ የትጥቅ ግጭቶች ሳቢያ ጥቃቱ እየተባባሰ መምጣቱ ይነገራል። በአማራ ክልል ላለፉት ሁለት አመታት በፌደራል መንግስትና በፋኖ ሃይሎች መካከል እየተካሄደ ያለው ግጭትም በሴቶች ላይ የሚደርሰውን ወሲባዊ ጥቃት ማባባሱን የቅርብ ጊዜ ዘገባዎች ያመለክታሉ።
ዶቸ ቬለ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኀን ባለሥልጣን (EMA) ሀገር ውስጥ የሚገኙ ዘጠኝ ዘጋቢዎቹ ከሥራ መታገዳቸዉን ይቃወማል። የመገናኛ ብዙኀን ተቆጣጣሪዉ ባለሥልጣን ሐሙስ ዕለት DW -ለዶቼ ቬለ የአማርኛ ዝግጅት ክፍል በደብዳቤ እንዳሳወቀዉ፤ በኢትዮጵያ የዶቼ ቬለ ዘጋቢዎች የጋዜጠኝነት ሥራ «ለጊዜው» አግዷል።
የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የዶቼ ቬለ ዘጋቢዎችን ለጊዜው ማገዱን በደብዳቤ ዐሳወቀ። ባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ለዶቼ ቬለ በላከው ይፋዊ ደብዳቤ «በኢትዮጵያ የጀርመን ድምጽ አገልግሎት (DW) ቋሚ የዜና ወኪሎችን» ለጊዜው ማገዱን አመልክቷል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የ7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ ረቂቅ የጊዜ ሠሌዳ አስመልክቶ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር ምክክር ማድረጉን፤ በደሴ መምህራን ኮሌጅ የሚሰለጥኑ ተማሪዎች የሚሰጣቸው ወርሐዊ የቀለብ ገንዘብ በቂ ባለመሆኑ ለችግር መጋለጣቸውን እና የዶላር ጭማሪና የኑሮ ውድነት የሚሉ ተካተዋል።
የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ካቢኔ በዚሁ የትግራይ ኃይሎች ጥያቄዎች ጉዳይ አስቸኳይ ስብሰባ አድርጎ እንደነበር ይታወቃል ። ሲዘጋጅ መቆየቱ የተነገረለት «የትግራይ የፀጥታ ኃይሎች ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ» የሚል ረቂቅ ደንብም ወደሚመለከታቸው አካላት መምራቱ በወቅቱ ተገልጧል ።
የኢትዮጵያ ፌደራዊ መንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናት፣ የጦር አዛዦችና የአፋር ክልል ባለሥልጣናት ኤርትራ ድንበር አጠገብ የምትገኘዉን ሥልታዊቷን የቡሬ ከተማን መጎብኘታቸው ዛሬ ተዘግቧል ።
ባለፈው አንድ ሣምንት ንግድ ባንክ ዶላር የሚገዛበት እና የሚሸጥበት ተመን አምስት ብር ከ50 ሳንቲም ገደማ ከፍ ብሏል። የብሔራዊ ባንክ አመልካች ዕለታዊ የምንዛሪ ተመን በአንጻሩ 150 ብር ከ90 ሳንቲም ደርሷል። ብር በውጭ ምንዛሪ ገበያው መዳከሙን ሲቀጥል ብሔራዊ ባንክ እርምጃ ለመውሰድ በድጋሚ ዝቷል።
ዶክተር ያብባል የምጣኔ ሀብት ተመራማሪ ብቻ አይደሉም፤ካህንም ጭምር እንጂ። በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ደብረ ታቦር ከተማ ተወልደው ያደጉትና የ1ኛና የ2ተኛ ደረጃ ትምሕርታቸውን የተከታተሉት ያብባል 2ተኛ ደረጃን እስኪጨርሱ ድረስ ትኩረታቸው በቀለም ትምሕርት ላይ ብቻ ነበር። ዩኒቨርስቲ ከገቡ በኋላ ግን የቤተ ክህነት ትምሕርትም ቀልባቸውን ሳበ።
ትግራይ ለጋዜጠኞች አደገኛ መሆኗ ቀጥሏል ሲል ዓለም አቀፉ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅት CPJ አስታውቋል።CPJ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ አለ ያለውን የፕሬስ ነጻነት ገደብም ሲያወግዝ ቆይቷል። ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ወደ ሌላ ግጭት በመግባት ተጨማሪ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች እንዳይደርሱ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ስጋታቸውን እየገለጹ ነው።
በተፈረደባቸው የ5 ዓመት የእስር ቆይታ በሙሉ ሳርኮዚ ከታሰሩበት ክፍል አጠገብ ሆነው በቋሚነት ሁለት ፖሊሶች እንደሚጠብቋቸው የፈረንሳይ የሀገር ውስጥ ጉዳይ ሚኒስትር ላውረን ኑኔስ ዛሬ ተናግረዋል። የሳርኮዚ የእስር ጊዜ እንዲያጥር ይግባኝ ያሉት ጠበቆቻቸው በአንድ ወር ውስጥ ሊፈቱ ይችላሉ ብለው ተስፋ ያደርጋሉ።
loading
Comments