ትኩረት በአፍሪቃ | Deutsche Welle

አፍሪቃን የሚመለከቱ ጉዳዮች ይታዩበታል።

የኮትዲቫር ምርጫ እና የዴሞክራሲ ጥያቄ

30 ሚሊዮን ነዋሪ ያላት ምዕራብ አፍሪቃዊቷ ኮትዲቫር ቅዳሜ፤ ጥቅምት 15 ቀን፣ 2018 ዓ.ም ፕሬዚደንታዊ ምርጫ አካሂዳለች ። ለአራተኛ ጊዜ የተወዳደሩት ፕሬዚደንት አላሳን ዋታራ ያሸንፋሉ የሚል ቅድመ ግምት ተሰጥቷል ። የ83 ዓመቱ አዛውንት የአገሪቱ ፕሬዚደንት አላሳን ዋታራን ጨምሮ አምስት ተፎካካሪዎች ለፕሬዚደንትነት ተፎካክረዋል

10-25
06:36

ከ18 ዓመት በታች ስደተኞች የሊቢያና የባሕር ላይ መከራ

ስደተኞችን ከመስጠም አደጋ የሚታደጉ የባሕር ላይ ነፍስ አድን ድርጅቶች የማንቂያ ደውሉን እያሰሙ ነው ። በርካታ ሕጻናት እና ወጣቶች በዓለም ላይ ካሉ አደገኛ የስደት መስመሮች አንዱ የሆነውን የሜዲትራኒያንን ባሕር አቋርጠው እየፈለሱ ነው ። በባሕር ከመስጠም ከተረፉት መካከል አንድ አምስተኛው የሚሆኑት ከ18 ዓመት በታች ናቸው ።

10-25
07:20

ትኩረት በአፍሪካ የጥቅምት 08 ቀን 2018 የዓለም ዜና

አምስት ጊዜ ለፕሬዝደንትነት ተወዳድረው ባይሳካላቸውም ራይላ ኦዲንጋ የኬንያን ዴሞክራሲ እና ምርጫ የይስሙላ እንዳሆን ከፍ ያለ ሚና ተጫውተዋል። በ80 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኦዲንጋ በተቃዋሚነታቸው ታስረዋል፤ ተገርፈዋል፤ ተሰደዋል። ግን እስከ መጨረሻው አላፈገፈጉም። በማዳጋስካር ጦር ሠራዊት ውስጥ ካፕሳት ተብሎ የሚጠራው ልዩ ኃይል አዛዥ ኮሎኔል ሚካኤል ራንጄሬሪና ፕሬዝደንት ሆነው ቃለ-መሐላ ፈጽመዋል። የ51 ዓመቱ የጦር መኮንን ሥልጣን የጨበጡት ለሦስት ሣምንታት ከተካሔደ የወጣቶች ተቃውሞ በኋላ ፕሬዝደንት አንድሬ ራጄሊና ከሥልጣን ተባረው ነው።

10-18
14:44

የካሜሩን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ለ43 ዓመታት ሀገሪቱን የመሩትን የፓል ቢያን ሥልጣን ያራዝም ይሆን ?

ፎኩም «በምርጫው ቀን ለመምረጥ መውጣት መቻላችንን መጠየቅ ጀምሬያለሁ፣ሁሉ ነገር ከተዘጋጋ ድምጽ ለመስጠት ወደምርጫ ጣቢያ እንዴት እንሄዳለን» ይላሉ።«የመራጮች ቁጥር በፀጥታ እጦት ካነሰ ምርጫው የተሀድሶ መንገድ ሳይሆን “የይስሙላ” ነው የሚለውን ግንዛቤ ያጠናክራል ፤መራጮች እንቅፋቶችን ከተቃወሙ ግን ያልተጠበቀ ለውጥ ሊያስከትል ይችላል ብለዋል።»

10-11
11:22

ትኩረት በአፍሪካ፤ የማቻር ፍርድ ቤት መቅረብ፤ ኡጋንዳ 40 ዓመታት በዩዌሪ ሙሰቬኒ ሥር

የማቻር ፍርድ ቤት መቅረብ ተጨምሮበት ደቡብ ሱዳንን እንደገና ወደ ግጭት ሊመልሳት ይችላል እየተባለ ነው። ለዛም ነው የሪክ ማቻር የፍርድ ሂደት የእሳቸውና እና የተባባሪዎቻቸው ብቻ ሳይሆን የደቡብ ሱዳን የወደፊት እጣ ፈንታን የሚወስን ነው የሚባለው።

09-27
13:02

የሳህል ግዛቶች ህብረት፤ አንድነት ወይስ እኩል ያልሆነ አጋርነት?

የማሊ፣ ኒጀር እና የቡርኪናፋሶ መንግሥታ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከተገረሱ በኋላ ከሁለት ዓመታት በፊት የተመሰረተዉ የሳህል ግዛቶች ህብረት (AES) በያዘዉ ያልተሟሉ ግቦች እና የኢኮኖሚ ተስፋዎች ብሎም ሚዛናዊ ያልሆኑ ጥቅሞች በማሊ፣ ኒጀር እና ቡርኪናፋሶ ትችቶች ገጥሞታል። ህብረቱ ዛሬ እስከ ምን ድርሶ ይሆን?

09-20
05:25

ስለደካማዉ የደቡብ ሱዳን የሰላም ስምምነት ምን ያዉቃሉ?

ደቡብ ሱዳን አዲስ የእርስ በርስ ግጭት አፋፍ ላይ ያለች ይመስላል። ከጎርጎረሳዉያኑ 2018 ጀምሮ በሃገሪቱ የነበረዉን ከፍተኛ የእርስ በእርስ ጦርነት ያስቆመዉ የሰላም ስምምነት በተለይ ምክትል ፕሬዝዳንት ሪክ ማቻር በአገር ክህደት እና በሌሎች ወንጀሎች ከተከሰሱ እና እስር ላይ ከዋሉ በኋላ የሰላም ስምምነቱ ዳመና ያጠላበት ይመስላል።

09-20
06:36

የኬንያው መሪ በጅምላ የፓርላማ አባላትን በሙስና መውቀሳቸው እያወዛገበ ነው

የኬንያ ፕሬዝዳንት የፓርላማ አባላቱን ጉቦ እየተቀበሉ ነው ብለው በጅምላ ከወቀሱ ወዲህ፤ የኬንያን ፖለቲከኞችን እያወዛገበ ነው። በሀገሪቱ የተደረገ አዲስ ጥናት እንዳመለከተው ዜጎች መሰረታዊ አገልግሎቶችን ለማግኘት ብቻ ጎቦ ለመስጠት ይገደዳሉ። በኬንያ በየዓመቱ ወደ 1.5 ቢሊዮን ዶላር ከዝርፊያ እና ከህገወጥ የገንዘብ ፍሰት እንሚጠፋ ይገመታል።

08-30
05:39

በደቡብ ሱዳን በበረታ ግጭት እና ፖለቲካዊ ቀውስ ሰላም እየተሸረሸረ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት አስጠነቀቀ

የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር ሚያርዲት በአምስት ዓመታት ውስጥ ሰባተኛ የፋይናንስ ሚኒስትር ሾመዋል። ልጃቸው አዱት ሳልቫ ኪር ሚያርዲት ፕሬዝዳንታዊ አማካሪ ሆናለች። ኪር ተቀናቃኛቸው ሪየክ ማቻርን አስረው ሹም ሹር ሲያካሒዱ በግጭት እና ፖለቲካዊ ቀውስ የሀገሪቱ ሰላም እየተሸረሸረ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት አስጠንቅቋል።

08-23
07:47

በአፍሪካ ክትባቶች በብዛት ለማምረት የተወጠነው ዕቅድ ከምን ደረሰ?

የኮቪድ-19 ዓለምን ካመሰ በኋላ የተሠሩ ክትባቶች በፍጥነት እና በፍትኃዊነት አለመዳረሳቸው የአፍሪካን ጥገኝነት አጋልጦታል። ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወዲህ አፍሪካ ክትባቶች እና መድሐኒቶች በማምረት ከጥገኝነት እንድትላቀቅ በርካታ ዕቅዶች አሉ። ዕቅዶቹ በረዥም ጊዜ ምን ያክል ዘላቂ ናቸው?

08-23
08:26

ትኩረት በአፍሪካ፦ የተባበሩት መንግሥታት ለደቡብ ሱዳን የሰጠው ማስጠንቀቂያ እና አፍሪካ ክትባቶች ለማምረት የጀመረችው ጥረት

የደቡብ ሱዳን ፕሬዝደንት ሳልቫ ኪር ሚያርዲት በአምስት ዓመታት ውስጥ ሰባተኛ የፋይናንስ ሚኒስትር ሾመዋል። ልጃቸው አዱት ሳልቫ ኪር ሚያርዲት ፕሬዝዳንታዊ አማካሪ ሆናለች። ኪር ተቀናቃኛቸው ሪየክ ማቻርን አስረው ሹም ሹር ሲያካሒዱ በግጭት እና ፖለቲካዊ ቀውስ የሀገሪቱ ሰላም እየተሸረሸረ መሆኑን የተባበሩት መንግሥታት አስጠንቅቋል። የኮቪድ-19 ዓለምን ካመሰ በኋላ የተሠሩ ክትባቶች በፍጥነት እና በፍትኃዊነት አለመዳረሳቸው የአፍሪካን ጥገኝነት አጋልጦታል። ከኮቪድ-19 ወረርሽኝ ወዲህ አፍሪካ ክትባቶች እና መድሐኒቶች በማምረት ከጥገኝነት እንድትላቀቅ በርካታ ዕቅዶች አሉ። ዕቅዶቹ በረዥም ጊዜ ምን ያክል ዘላቂ ናቸው?

08-23
16:25

በተቃዋሚዎች ላይ የአዕምሮ መታወክ ያስከተለው የኬንያ ተቃዉሞ እና የዛምቢያ የሳይበር ህግ ድጋፍ እና ተቃዉሞ

ለተቃዉሞ አደባባይ የወጡ እና ለፖሊስ የጭካኔ ጥቃት የተጋለጡ ኬንያዉያን ተቃዋሚዎች ለከፋ የአዕምሮ መታወክ እየተጋለጡ ነው። ጠበቅ ያለ የሳይበር ደህንነት ህግን ተግባራዊ ያደረጉት የዛምብያው ፕሬዚዳንት በድጋፍ እና ተቃዉሞ መሃል ናቸው

07-12
10:51

Recommend Channels