Discover
ዜና መጽሔት
ዜና መጽሔት
Author: DW
Subscribed: 4Played: 428Subscribe
Share
© 2025 DW
Description
በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። በዐበይት የኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓ እና የዓለም ጉዳዮች ላይ ዜናዎች፣ ቃለ-መጠይቆች እና ጥልቅ ትንታኔዎች ይቀርባሉ። ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ የዶይቼ ቬለ ዘጋቢዎች የሚያጠናቅሩት ዜና መፅሔት ከሰኞ እስከ አርብ ከዓለም ዜና ቀጥሎ ይቀርባል። የዶይቼ ቬለን ሥርጭት በራዲዮ፣ በሳተላይት እና በፌስቡክ በቀጥታ ማድመጥ ይቻላል። በአፕል ፖድካስት እና በስፖቲፋይ የዶይቼ ቬለን ዜና መጽሔቶች ያዳምጡ።
610 Episodes
Reverse
የዛሬው የዜና መጽሔት ፤ ፤የኢትዮጵያ ሙስሊምን ከትምህርት እና ሀገራዊ ተሳትፎ በማራቅ ዘላቂ ልማት አይኖርም ሲል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ማስታወቁ ፤ቡለን ወረዳ ባለፈው ቅዳሜ ማለዳ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት በርካታ ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸዉ ፤ እንዲሁም በአዉሮጳ ኅብረት ተቃዉሞ የገጠመዉ የአሜሪካ የ 28 ነጥብ የሰላም እቅድ ለዩክሬይን የተሰኙ ርዕሶችንበስፋት ያስቃኘናል።
በዛሬው የዜና መጽሔት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ለመጀመሪያ ጊዜ የ520 ሚሊዮን ዶላር ስምንት ጨረታዎች ይፋ ማድረጉ፤ደቡብ አፍሪቃ የምታስተናግደው በአፍሪቃ የመጀመሪያው የቡድን ሀያ ጉባኤ፤ የዓለም ባንክ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸዉ ሃገራት ለጤና ጥበቃ የሚመድቡት ገንዘብ እጅግ ዝቅተኛ ነዉ ማለቱ እንዲሁም፤ ፓሪስ ላይ የተካሄደዉ የጀርመን ፈረንሳይ ትብብር ጉባኤየተሰኙ ርዕሶችን ያስቃኘናል።
በኢትዮጵያ የፀጥታ እና የፖለቲካ ጥያቄዎች መልስ ካላገኙ ቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ምርጫ ሊሆን አይችልም ሲሉ የኦፌኮ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና ለዶቼቬለ ተናግረዋል። በደቡብ ወሎ ዞን ሐይቅ እና ዉጫሌ ከተሞች አቅራቢያ የተጠለሉ ተፈናቃዮች አቤቱታ አቅርበዋል። እናት ፓርቲ ፣ከተጣመርኩበት «ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት» ከተባለው ቅንጅት፣ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰርዞኛል ሲል ወቅሷል። እነዚህና የአውሮፓ ኅብረት አባል ሀገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ዛሬ ያካሄዱት ስብሰባ የዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅታችን የሚያተኩርባቸው ጉዳዮች ናቸው።
የዕለቱ መጽሔታችን ሦስት ርዕሰ ጉዳዮችን በቅደም ተከተል ያስደምጣል። ከምርጫ በፊት ሰላም እንዲሰፍን ፣የታሰሩ ፖለቲከኞች እና ጋዜጠኞች እንዲፈቱ መጠየቁ፣ ዩናይትድ ስቴትስና ሳዑዲ አረቢያ በንግድ፣ በቴክኖሎጂ፣ በጦር መሳሪያ ሽያጭና በመከላከያ ያላቸዉን ትብብር ለማጠናከር መስማማታቸው፣ እንዲሁም የጄፌሪ ኤፕስታይን የወሲብ ቅሌት ሰነድ ይፋ እንዲሆን መወሰኑ እና አንድምታውን የተመለከቱ ዘገባዎች በዝርዝር የሚቀርቡ ርዕሰ ጉዳዮቻችን ናቸው ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምክክር የገጠሙት ተግዳሮቶች “ፖለቲካዊ መፍትሔ ያስፈልጋቸዋል”መባሉ
ቢያንስ አምስት ኢትዮጵያዊያን በአንድ ሳምንት ውስጥ ደቡብ አፍሪቃ ውስጥ ተገድለዋል
የጋዜጠኛ እና ደራሲ ዜናነህ መኮንን 1ኛ ዓመት መታሰቢያ
የዓለም ዜናን በሚከተለው የዜና መጽሔት በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጂንካ ከተማ መከሰቱ የተሰማው የ«ቫይራል ሄመሬጂክ ፊቨር» ጉዳይ ፣ በታንዛኒያ ምርጫ ከደረሰው ግጭት በኋላ ፖሊስ ስለወሰዳቸው ርምጃዎች የወጡ አዳዲስ መረጃዎች እንዲሁም በጀርመን የታሰበው ፈቃደኛነትን መሠረት ያደረገ ብሔራዊ ውትድርና የተሰኙት ርዕሶች ይተነተናሉ
በዜና መፅሔቱ በጅንካ ከተማ የተከሰተው በሽታ፤ ፈረንሳይ የዛሬ 10 ዓመት የበርካቶችን ሕይወት የቀጠፉ የሽብር ጥቃቶች የተፈጸሙበትን ዕለት አስባ መዋሉዋ እንዲሁም የኢራንና የዓለም የአቶሚክ ተቆጣጣሪ ድርጅት ዉዝግብን የሚያስቃኙ ዘገባዎችን አካቷል።
የዓለም ዜናን በሚከተለው የዜና መፅሔት ፣ ተቃውሚ ፓርቲዎች ከመጭው የኢትዮጵያ ምርጫ በፊት ምቹ ሁኔታ እንዲፈጠር መጠየቃቸውን ፣ ኢትዮጵያ COP32 እንድታስተናግድ መመረጧን ፣ የተባበሩት አረብ ኢመሬቶች በሌሎች ሀጋራት ያላትን ተፅዕኖ እንዲሁም የትራምፕ አስተዳደር አዳዲስ የስደተኞች ፖሊሲዎችና አንደምታቸውን የሚያስቃኙ አራት ዘገባዎች አሉን
በትግራይ ክልልና ባካባቢዉ ያንዣበበዉን የጦርነት ሥጋት፣
ብራዚል ዉስጥ በተያዘዉ የዓየር ንብረት ለዉጥ ጉባኤ የአፍሪቃ ወጣቶች ሚና፣
የሩሲያ ሰዉ አልባ አዉሮፕላኖች ቤልጂግ አየር ክልል አንዣበቡ መባሉ ያስከተለዉ ሥጋት፣
የአሜሪካ መንግሥት መዘጋት የመነሳቱ ተስፋ
የዜና መፅሔት ዝግጅታችን
በትግራይ ክልልና ባካባቢዉ ያንዣበበዉ ሥጋት፣
የትግራይ ሙሕራንና ባለሙያዎች ማሕበር የሰላም ጥሪ፣
የሱዳን የርስበርስ ጦርነትና የርዕሠ ከተማ ካርቱም መደብደብን ያስተነትናል።
የዛሬው የዜና መፅሄት፤ በአፋር ክልል በትግራይ ሀይሎች የቀሰቀሱት ግጭት፤ ፤የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት፣ ከ7ኛው አገር አቀፍ ምርጫ በፊት የሕገመንግሥት ማሻሻያ እንዲደረግ መጠየቃቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሸሪያ በሚመሩ ባንኮች ላይ የጣለውን ገደብ ማንሳቱን እንዲሁም የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮጳ ኢትዮጵያ የኢንቬስትመንት መድረክን ያስቃኛል።
በኪረሙ ወረዳ ታጣቂዎች ባደረሱት ጥቃት አራት ሰላማዊ ሰዎች ተገደሉ መባሉ፤
«ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል» የተባለው የሱዳን ጦርነት፣
የጀርመን መራሄ መንግሥት ለምን የሶርያ ስደተኞች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ አሳሰቡ
በኒውዮርክ ምርጫ የግራ ክንፍ ፖለቲከኛ በከንቲባነት ማሸነፋቸው
የዜና መፅሔታችን መንግሥት እና በህወሓት መካከል ከምርጫ በፊት ፖለቲካዊ ውይይት እንዲጀመር የቀረበው ጥሪ፤ ለመጪው ሀገራዊ ምርጫ አስቻይ ኹኔታዎች እንዲኖሩ የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባር ኦነግ መጠየቁ፤ እንዲሁም ለትራምፕ ዛቻ የናይጀሪያ ምላሽ የሚመለከቱ ዘገባዎችን አካቷል የዜና መጽሔት
ከዕለተ ሰኞ ሳምንታዊ መሰናዶዎች ቀዳሚው ማኅደረ ዜና የሱዳንን ቀውስ ይቃኛል።
ዜና መጽሔት ዛሬ ፤
ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ በየመን ስደተኞች የተገደሉበት የአሜሪካ ጥቃት “እንደ የጦር ወንጀል” እንዲመረመር መጠየቁ
የኤርትራዉ ፕሬዚዳንት የአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ የአምስ ት ቀናት የግብፅ ጉብኝት ፤ እና አንድምታዉ እንዲሁም
አፍሪካውያን ተማሪዎች ለምን የሩሲያን ዩንቨርስቲዎች ይመርጣሉ? የተሰኙ ርዕሶችን ያስቃኘናል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ትናንት በሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ተገኝተው በሰጡት ገለጻ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎችን አስተያየት ጠይቀናል።
የብሪታንያ መንግሥት በሴቶች ላይ የወሲብ ጥቃትና ትንኮሳ በመፈጸም ተከሶ በአንድ የብሪታንያ ፍርድ ቤት እስርና ወደ ሀገሩ መባረር የተበየነበትን ሀዱሽ ገብረሥላሴ ቅባቱን ወደ ኢትዮጵያ ማባረሩን ዛሬ አስታውቋል። ጀርመን ውስጥ ይፋ የሆነ አንድ ጥናት ጀርመን ውስጥ በርካታ ሴቶች ከቤት ውጪ ደኅንነት እንደማይሰማቸው ማመልከቱን መነሻ ያደረገ ሌላ ዘገባ በዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅታችን ተካተዋል።
የዜና መፅሔት ዝግጅታችን የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ከሐገሪቱ የምክር ቤት አባላት ለቀረቡ ጥያቄዎች የሰጡትን መልስና ማብራቂያ የሚዳስሰዉን ዘገባ ያስቀድማል።ዜና መፅሔቱ የምሥራቅ ኢትዮጵያ የፀጥታ የጋራ ግብረ-ኃይል ከ40 በላይ የአማፂ ቡድን መሪና አባላትን ገደልኩ ማለቱን የሚቃኝ ዘገባም አለዉ።የሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ መሸለምና የሱዳን ጦርነትንም የሚመለከቱ ዘገቦች አሉትም።






















