DW Amharic የሕዳር 6 ቀን 2018 የዓለም ዜና
Update: 2025-11-15
Description
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የተከሰተው የሔሞራጅ ትኩሳት በሽታ መንስዔ የማርበርግ ቫይረስ መሆኑን የጤና ሚኒስቴር አረጋገጠ። በኢትዮጵያ የሚካሔደው ሀገራዊ ምክክር ያጋጠሙት “አብዛኞቹ ተግዳሮቶች ፖለቲካዊ በመሆናቸው ፖለቲካዊ መፍትሔ” እንደሚያስፈልጋቸው ፕሮፌሰር መስፍን አርዓያ አሳሰቡ። ከሱዳን ሕዝብ ከግማሽ በላይ የሚሆነው ሰብአዊ ርዳታ ያስፈልገዋል ተባለ። ሱዳን እና ደቡብ ሱዳን በይገባኛል በሚወዛገቡባት አቢዬ ግዛት የሰፈረውን ሰላም አስከባሪ የሥራ ዘመን የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ጥበቃ ምክር ቤት አራዘመ። ደቡብ አፍሪካ በኬንያ በኩል ወደ ጁሐንስበርግ የተጓዙ ፍልስጤማውያንን ጉዳይ እንደምትመረምር አስታወቀች።
Comments
In Channel






















