የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአውሮጳ ኢትዮጵያ የኢንቬስትመንት መድረክ
Update: 2025-11-06
Description
የ75 ዓመት ስኬታማ ጉዞ ባለቤትየኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ እንደሚያስገነባው የሚጠበቀው አዲሱ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ አስራ ሁለት ቢሊዮን ዶላር ሊያስወጣው እንደሚችል ተነግሯል። ፕሮጀክቱ የአየር መንገዱ ታላቅ እምረታ ብቻ ሳይሆን የአፍሪቃን የአየር ትራንስፖርት ወደ አዲስ ምዕራፍ እንደሚያሸጋግረው የሚጠበቅ ነው ተብሏል።
ከአፍሪቃ ልማት ባንክ ባሻገር አሜሪካም ፕሮጀክቱን በገንዘብ ለመደገፍ ፍላጎት እንዳላት አስታውቃለች።
ሰሞኑን በፓሪስ ከተማ በተካሄደው የአውሮፓ ኢትዮጵያ የኢንቬስትመንት መድረክ ላይም ቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ስራ ግንባታን ለመደገፍና በስራው ላይም ለመሳተፍ ኤርባስና ሌሎችም የአውሮጳ ኩባንያዎች ከፍተኛ ፍላጎት ማሳየታቸው ታውቋል። ይህም ረዥም ዓመታትን በንግድ ትስስር ከቦይንግ ጋር የዘለቀው የኢትዮያ አየር መንገድ አሁን ከኤርባስ ጋር እየተጠናከረ እንደሚሄድ ይጠበቃል። የንግድ ግንኙነትን ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለውን የገበያ ፉክክር በምን መልኩ ሊያስተናግደው ይችል ይሆን ?
ሃይማኖት ጥሩነህ
ኂሩት መለሰ
እሸቴ በቀለ
Comments
In Channel























