አንድ ለአንድ፤ ከሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ጋር
Update: 2024-12-13
Description
በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ከውትድርና አንስተው በዘመነ ደርግም በተለያዩ የመንግሥት ኃላፊነቶች ለዓመታት ኢትዮጵያን አገልግለዋል። የሐረር ጦር አካዳሚ ሁለተኛ ኮርስ ምሩቅ ናቸው። በሀገር ውስጥና በውጭ ዩኒቨርሲቲዎች ሕግን ተምረዋል አጥንተዋል። በደርግ ዘመነ ሥልጣን በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በእርዳታ ማስተባበሪያ ኮሚሽን፤ እንዲሁም በዘመቻ መምሪያ በኃላፊነት አገልግለዋል። ከሀገር ከተሰደዱ በኋላም በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ስር በተለያዩ የአፍሪቃ ሃገራት በልዩ ልዩ መስኮች ሠርተዋል። አሁኑ ሙሉ ጊዜያቸውን የአፍሪቃ ስትራቴጂ እና የጸጥታ ጥናት ተቋምን በመምራት ምርምሮችን ያካሂዳሉ። ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ ግለታሪካቸውን ጨምሮ የተለያዩ መጽሐፍትን ለንባብ አብቅተዋል።
ቃለምልልሱን ለማድመጥ የድምፅ ማዕቀፉን ይጫኑ
ሸዋዬ ለገሠ
Comments
In Channel