DiscoverDW | Amharic - Newsየጀርመን ፕሬዝደንት ይቅርታ ጠየቁ
የጀርመን ፕሬዝደንት ይቅርታ ጠየቁ

የጀርመን ፕሬዝደንት ይቅርታ ጠየቁ

Update: 2023-11-01
Share

Description

የጀርመን ፕሬዝደንት ፍራንክ ቫልተር ሽታይንማይር ሐገራቸዉ ታንዚያን ቅኝ ትገዛ በነበረበት ዘመን በታዚኒያ ሕዝብ ላይ ባደረሰችዉ ግፍ «ማፈራቸዉን» አስታወቁ።ጀርመን የዛሬዋን ታንዛኒያን ቅኝ በገዛችበት ዘመን የጀርመን ጦር ለነፃነት ያመፁ በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ የሐገሬዉን ተወላጆች መገደሉ ተረጋግጧል።ታንዛኒያ እንደምትለዉ በተለይ እንደ ግሪጎሪያኑ አቆጣጠር ከ1905 እስከ እስከ 1907 ድረስ ቅኝ ገዢዉ ጦር በከፈተዉ ጥቃት እስከ 300 ሺሕ የሚደርሱ የታንዛኒያ ዜጎች በግፍ ተገድለዋል።ከትናንት ጀምሮ ታንዛኒያን በመጎብኘት ላይ የሚገኙት ፕሬዝደንት ሽታይማየር ዛሬ በርካታ ሰዎች ከተገደሉባቸዉ አካባቢዎች ሶንጌ የተባለዉን አካባቢ ሲጎበኙ የጀርመን ቅኝ ገዢዎች ላደረሱት ግፍ በይፋ ይቅርታ ጠይቀዋል። ሽታይንማየር የጀርመን ቅኝ ገዢ ጦር የረሸናቸዉን የያኔዉን ባላባት የሶናጌ ምባኖና የ66 ተከታዮቻቸዉን የልጅ-ልጅ ልጆችና ዘመዶች አነጋግረዋልም።በታንዛኒያ የነፃነት ንቅናቄ ስም ማጂ፣ ማጂ ተብሎ የተሰየመዉን ቤተ-መዘክርም ጎብኝተዋል።ጀርመን፣ የተገደሉ ሰዎች ዝርያዎችን ሐዘን እንደምትጋራና ሐዘኑን እንዲወጡ አብራቸዉ እንደምትቆም ፕሬዝደንቱ አረጋግጠዋል።ጀርመን በመጀመሪያዉ የዓለም ጦርነት ስትሸነፍ የዛሬዎቹን ታንዛኒያ፣ ሩዋንዳና ብሩንዲን የሚያስተናብረዉ «የጀርመን የምስራቅ አፍሪቃ« ይባል የነበረዉ የቅኝ ግዛት ዘመንም አብሮ አብቅቷል።



ነጋሽ መሐመድ



ኂሩት መለሰ

Comments 
In Channel
loading
00:00
00:00
x

0.5x

0.8x

1.0x

1.25x

1.5x

2.0x

3.0x

Sleep Timer

Off

End of Episode

5 Minutes

10 Minutes

15 Minutes

30 Minutes

45 Minutes

60 Minutes

120 Minutes

የጀርመን ፕሬዝደንት ይቅርታ ጠየቁ

የጀርመን ፕሬዝደንት ይቅርታ ጠየቁ